የአፍሪካ ህብረት ኢትዮጵያዊ የደህንነት ኃላፊውን ከስራ ማሰናበቱን ገለጸ።

የህብረቱ የደህንነት ኃላፊ የነበሩት ሜጀር ጄነራል ገ/እግዚአብሔር መብራቱ መለስ ኢትዮጵያ የታማኝነት ጥያቄ ስላነሳችበት ከስራው እንዲሰናበት ማድረጉን የአፍሪካ ህብረት አስታወቀ።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መሀመት ኅዳር 2 ቀን 2013 ዓ.ም ለሜጀር ጄነራል ገ/እግዚአብሔር መብራቱ መለስ የስራ ስንብት ደብዳቤ መስጠታቸው ተገልጿል፡፡

ውሳኔው የኢትዮጵያ መንግስት በግለሰቡ እምነት እንደሌለው ከአንድ ቀን በፊት ካስታወቀ በኋላ የመጣ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

By Eyasu Esayas

Entrepreneur, Writer, Business advocate and Teacher. Nice to have every soul on board.

Leave a Reply